የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ተምህርት እና ቴ/ሙ/ት/ስ/ተ/ማህበር ቅዳሜ 26/02/2015 ዓ.ም በማግኖሊያ ሆቴል እና ኮንፈረንስ ሴንተር ባካሄደው ዓመታዊ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በልዩ ልዩ አጀንዳዎች ላይ ውይይት ያከሄደ ሲሆን በመጨረሻ ማህበሩን በቀጣይ 3 ዓመታት በበላይነት የሚመሩ ስራ አመራር ቦርድ በማህበሩ መተዳደሪያ ደንብ መሰረተ ምርጫ አካሂደዋል። በዚህ መሰረት:-
- ዶ/ር አረጋ ይርዳው ከዩኒቲ ዩኒቨርሲቲ ፕረዚደንት
- አቶ ፈይሳ አራርሳ ከሐራምቤ ዩኒቨርሲቲ ም/ፕረዚደንት
- ዶ/ር ገበያው ጥሩነህ ከጋምቢ ኮሌጅ
- ደ/ር አበበ ደምሴ ከሲፒዩ ኮሌጅ
- ደ/ር ማቲዎስ ግችሌ ከኒው ጀኔሬሽን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ
- ደ/ር ተረፈ ከሆፕ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ
- ዶ/ር ናስር ከሂልኮ ኮሌጅ
- ዶ/ር አያና ከቪክትሪ ኮሌጅ
- አንድ ተወካይ ከአማራ ክልል የማህበሩ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የተመረጡ ሲሆን ነባሩን አመራር በማመስገን የእለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።